Posted in ዋልድባ ገዳም on 12/13/2013|
Leave a Comment »
|
ዋልድባ |
- · ዘራቸውን እንደጣዖት የሚያመልኩ ካሕናት ተብዪውች ዋልድባን የመታደግ ጥረትን ለማደናቀፍ እየሞከሩ ነው
- · በዋልድባ የቤተ ጣዕመ ክርስቶስ አባቶች ልማት አንቃወምም፥ ገዳሙንም አይነካም በማለት የአዞ እንባ እያነቡ ነው
- · አፍቃሪ መንግሥት (ካድሬዎች) ዋልድባን ለመርዳት የሚደረገውን ጥረት ለመቃወም በየመንደሩ አሉባልታ እየነዙ ይገኛሉ
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም የኢትዮጵያ መንግሥት ታሪካዊውን እና ጥንታዊውን የዋልድባ ገዳም አፍርሶ የስኳር ፋብሪካ ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንደገዳማዊ ገዳማውያን የሚባሉ፣ ነገር ግን ዘራቸውን እንደጣዖት የሚያመልኩ የበግ ለምድ ለብሰው በጠቦቶች መካከል የሚዘዋወሩ ተኩላዎች፥ ይህንን ታሪካዊ እና ጥንታዊ ገዳም ለመታደግ የሚንቀሳቀሰውን ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች አንድነት (ዋልድባን እንታደግ) በመባል የሚታወቀውን ተቋም የተለያየ አሉባልታ በመንዛት ጥረቱን ለማደናቀፍ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ለመረዳት ችለናል።
ይህ ተቋም ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በተለያየ ጊዜ የዋልባ ገዳም አባቶች ላይ የመንግሥት ካድሬዎች የሚያደርሱባቸውን እንግልት፣ በደል፣ እና ስደት አቅም በፈቀደ ለመርዳት ይህ ተቋም ብዙ ጥረቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ከነዚህም ጥረቶች መካከል ለመጥቀስ ያህል
፩ኛ/ ለአበረንታት መድኅኒዓለም ገዳም ለመርዳት $6000.00
፪ኛ/ ለዳልሻህ ኪዳነ ምሕረት ገዳም $3000.00
፫ኛ/ ለሰቋር ኪዳነ ምሕረት የእናቶች ገዳም መርጃ $2500.00
፬ኛ/ አባቶች እና እናቶች ወደጎንደር በተሰደዱ ጊዜ ለእህል ውሃ ማቅመሻ $500.00
፭ኛ/ እናቶች በአዲስ አበባ እርዳታ ለመጠየቅ በሄዱበት ወቅት ለእናቶች መርጃ የተላከ $800.00
፮ኛ/ ለዳልሻሕ ኪዳነ ምሕረት እናቶች ገዳም መርጃ የተላከ $4000.00
በጠቅላላ ለዋልድባ ገዳም የተላከው የገንዘብ መጠን እስከ ዛሬ ድረስ $16,800.00 መላኩን በመረጃዎች የተደገፈ ማስረጃዎች በእጃችን አሉ ነገር ግን እነዚህ ለመንግሥት እና ለቤተክርስቲያን ደብል ኤጀንት ሆነው እየሰሩ የሚገኙ ከሃይማኖታቸው ይበልጥ ለዘራቸው እና ለጎጣቸው አመዝነው በአብዛኛው ጊዜ ይህንን ጥረት ለመቃወም በተለያየ አውደ ምሕረት ላይ የሚናገሯቸው ነገሮች በእጅጉ የእነዚህን ዘረኞች ማንነት ልንመረመምር እና ልናውቃቸው እንደሚገባን ከወዲሁ ለመረዳት ችለናል። እነዚህ ሰዎች በየመንደሩ እየዞሩ፣ በየንሰሐ ልጆቻቸው ቤት በመሄድ እንዲሁም አጋጣሚውን ባገኙት ጊዜ ሁሉ ከሚናገሯቸው ንግግሮች መካከል ለአብነት ለመጥቀስ ያህል:
(more…)
Read Full Post »