Feeds:
Posts
Comments

Archive for the ‘ከዚህም ከዚያም’ Category

ይድረስ የምለው:+

ለሰንበት ትምህርት  ቤቶች አንድነት ኅብረት

ለማኅበረ ቅዱሳን

ለማኅበራት ኅብረት

ለየ አጥቢያ ሰባክያነ ወንጌል

በግል ሚዲያም ላይ በአገልግሎትም የምትሳተፋ ወንድሞችና እህቶች ነው። 

መልእክት:-

የሀገራችን ጉዳይ ከድጡ ወደ ማጡ መጥቶ ዋናው አዘቅት ጫፍ ደርሷል። የቤተ ክርስቲያን ገዳይ ከሀገር ጉዳይ ለብቻ ለይቶ ማየት በጣም የበዛ የዋህነት ሳይሆን ሞኝነት ነው። ነቀርሳው ዋለልኝ እንዳለው “ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰብ እስር ቤት ናት” ያለው አሁን ነው የሆነው። ሁሉም እስር ቤት ገብቷል። 

(more…)

Read Full Post »

ሲኖዶስ አይሳሳትም፣ ፓትርያርክ አይሳሳትም የሚል አስተምህሮ የለንም። እንዲህ ዓይነት አመለካከት ያላቸው ካቶሊኮች ናቸው። ሲኖዶስም ይሳሳታል። በታሪክም የኬልቄዶን ሲኖዶስ ተሳስቶ ጉባኤው ራሱ ተወግዟል። ብዙ ፓትርያርኮች ተሳስተው ተወግዘዋል። በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የማይሳሳት እግዚአብሔር ነው። እንዲሁም የእርሱ አካል የሆነችዋ ቤተክርስቲያን አትሳሳትም። ሁልጊዜም ልክ ናት። ሲኖዶስ የማይሳሳት የመጨረሻ ወሳኝ አካል ስለሆነ ሁልጊዜ እንቀበለው አይባልም። ሲኖዶሱ ሲሳሳትም ስሕተቱን እናከብራለን እንቀበላለን አይባልም። ነውር ነው። ሲኖዶስ ራሱ በእግዚአብሔር ሕግ ይለካል። ከእግዚአብሔር ሕግ ካፈነገጠ ውሳኔው ተቀባይነት አይኖረውም።

(more…)

Read Full Post »

ንቀጽ ፬ ስለ ሊቃነ ጳጳሳት ይናገራል።

፩) ኤጲስ ቆጶስ፣ ጳጳስ፣ ሊቀ ጳጳሳት በመሾም በመሻር በማጥመቅ በማስተማር አንድ ናቸው።

                            

፪) ሊቀ ጳጳሳት ርእሰ ኤጲስ ቆጶሳት ይባላል። የሊቀ ጳጳስ ሹመቱ በምእመናን፣ በጳጳሳት፣ በኤጲስ ቆጶሳት ላይ ነው።

                            

፫) ሠለስቱ ምእት በዓለም ላይ አራት ፓትርያርኮች ይኑሩ ብለዋል። የሮም ፓትርያርክ የበላይ ሆኖ ይፍረድ፣ ሁለተኛ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ይፍረድ፣ ሦስተኛ የኤፌሶን ፓትርያርክ ይፍረድ፣ አራተኛ የአንጾኪያ ፓትርያርክ ይፍረድ ብለዋል። ብያኔ ፍርድ ለሮም፣ አፈ ጉባኤ ለእስክንድርያ፣ ቡራኬ ለኤፌሶን፣ ማዕጠንት ቅዳሴ ለአንጾኪያ ነበር።

                            

፬) የኤፌሶን ሊቀ ጵጵስና ወደ ቍስጥንጥንያ ትለፍ አሉ። ለነገሥታቱ ክብር ለካህናቱ ማዕርግ ትሆን ዘንድ። 

(more…)

Read Full Post »

ሢመተ ጵጵስና በትእዛዘ ብልጽግና

#ሰሞኑን በሕገ ወጥ መንገድ የጳጳስ ልብስ ለብሰው ጳጳስ በሉን እያሉ በመንግሥት ወታደሮች ክርስቲያኖችን ሲያስጨፈጭፉ የነበሩ አካላት በቤተ ክህነቱ ግቢ ማንዣበቡን ተያይዘውታል፡፡፡፡

ባለፈው የሐሰት እርቅ ስምምነት ጊዜም ጠቅላዩ ከእነዚህም መካከል የምትሾሙት ይኖራል በማለት ምክር መሰል ትእዛዝ አስተላልፏል፡፡

ሲመተ ጵጵስና እንዴት?

የጵጵስና መሠረቶቹ ሐዋርያት ናቸው፤ ከሐዋርያት መካከል  ክርስቶስን ካገኘ በኋላ ወደ ዓለም የተመለሰ ከይሁዳ በቀር አንድም ሐዋርያ የለም፡፡ መላ ሕይወታቸውን፣ መላ ዘመናቸውን የምሥራቹን ወንጌል ለሰው ልጆች ሁሉ ለማዳረስ በመንከራተት፣ በጾም እና በጸሎት፣ በፍጹም ተጋድሎና ትጋት እየኖሩ ምእመናን በበዙባቸው አካባቢዎች ሁሉ ጳጳሳትን እየሾሙ በሰማእትነት አልፈዋል፡፡

የሹመት መሥፈርታቸውም እንዲህ ይላል፡- ‹‹ወርቅ ወይም ብር ወይም ናስ በመቀነታችሁ፥

ወይም ለመንገድ ከረጢት ወይም ሁለት እጀ ጠባብ ወይም ጫማ ወይም በትር አታግኙ፤ ለሠራተኛ ምግቡ ይገባዋልና። በምትገቡባትም በማናቸይቱም ከተማ ወይም መንደር፥ በዚያ የሚገባው ማን እንደ ሆነ በጥንቃቄ መርምሩ፤ እስክትወጡም ድረስ በዚያ ተቀመጡ።››    ማቴ፡ 10፥9

‹‹መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል። እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል። ሞያተኛ ስለ ሆነ ለበጎቹም ስለማይገደው ሞያተኛው ይሸሻል።›› ዮሐ፡ 10 11››

(more…)

Read Full Post »

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 

ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ 

 ጥር 14 ቀን 2015ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ሕገወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመትን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥር 18 ቀን 2015ዓ.ም. ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የተከናወነው ድርጊት የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ፣ ቀኖና አስተዳደራዊ መዋቅር የጣሰ ሕገወጥ አድራጎት መሆኑን አጽንኦት ሰጥቶ በመወያየት ሕገወጡን ሹመት ያከናወኑትና ተሿሚዎችን በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት ከዲቁና ጀምሮ የነበራቸውን ማዕረገ ክህነት በሙሉ በመሻር ከቤተ ክርስቲያኒቱ አባልነት አውግዞ መለየቱ የሚታወስ ነው፡፡ 

ምንም እንኳን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በውሳኔው ውግዘቱ እንደተጠበቀ ሆኖ በድርጊታቸው ተጸጽተው እና ከስህተታቸው ተመልሰው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥርዓት መሠረት የሚሰጣቸውን ቀኖና ተቀብሎ ለመመለስ ዝግጁ ከሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ የይቅርታ በር ክፍት መሆኑን በማሳወቅ መግለጫ የሰጠ ቢሆንም ግለሰቦቹ ከስህተታቸው ተምረው በይቅርታ እድሉ ከመጠቀም ይልቅ በሕገወጥ መንገዱ ቀጥለውና ውግዘቱን ጥሰው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መዋቅራዊ አደረጃጀት መሠረት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በቅዱስ ሲኖዶስ ተመድበው በሚያገለግሉባቸው አህጉረ ስብከት ላይ እርስ በርሳቸው በመመዳደብ እያደረጉት የነበረውን ሕገወጥ እንቅስቃሴ መንግስት በሕግ የተጠላበትን ሕግን የማስከበር ኃላፊነት በመወጣት የቤተ ክርስቲያናችንን ተቋማዊ ልዕልና እንዲያስከብርልን ከመግለጫም አልፎ በደብዳቤ ያቀረብነው ጥያቄ ተቀባይነት አጥቶ በሕገወጥ መንገድ የተሾሙት ግለሰቦች በመንግሥታዊ የፀጥታ አካላት ታጅበው በኦሮምያ ክልል የሚገኙትን አህጉረ ስብከት፣ ወረዳ ቤተ ክህነት፣ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን በኃይል ሰብረው ተቋማቱን በመውረር ሀብትና ንብረት የተዘረፈ ሲሆን ይህም ሕገወጥ ድርጊት በሚከናወንበት ወቅት ሕገ ቤተ ክርስቲያናችን አይጣስም፣ ሲኖዶሳችን አይከፈልም፣ ቀኖናችን አይደፈርም በማለት በጽናትና በአንድነት ድርጊቱን የተቃወሙት ምዕመናን፣ ወጣቶችና አገልጋይ ካህናት እንዲሁም በየደረጃው ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልዩ ልዩ የሥራ ኃፊዎች በተለይም የሻሸመኔና አካባቢው ምእመናንና አገልጋይ ካህናት ለሞት፣ ለአካልና የሞራል ጉዳት፣ ለእስራትና እንግልት ተዳርገዋል፡፡  

(more…)

Read Full Post »

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመቐለ ከተማ ከዚህ ዓለም ድካም ባረፉት በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው ተገኝተው የብፁዕነታቸው ሽኝት በመገኘት አባታዊ ቡራኬያቸውን እና ጸሎት አድርሰው ወደ መንበረ ፕትርክናቸው ተመልሰዋል።

የብፁዕነታቸው በረከታቸው ይደርብን አሜን

Read Full Post »

ለአድዋ ጦርነት መነሳት ዋነኛ ምክንያት የሆነው የዉጫሌ ውል በሚያዚያ ፲፱፻፹፩ ዓ.ም በአሁኗ አምበሳል ወረዳ ውጫሌ በምትባል ቦታ በአጼ ምኒልክና በጣሊያኑ ንጉስ ኡምቤርቶ መካከል ተፈረመ፡፡

የውጫሌ ውል ፳ አንቀጾች ያሉት ሲሆን አንቀጽ ፲፯ ላይ የሰፈረው ጽሁፍ በኢትዮጵያ በኩል ተቀባይነት በማጣቱ ለጦርነቱ መቀስቀስ ምክንያት ሆኗል፡፡

አንቀጽ ፲፯ በአማርኛ “የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ከአውሮፓ ነገስታት ለሚፈልጉት ጉዳይ ሁሉ በኢጣሊያ መንግስት አጋዥነት መላላክ ይቻላቸዋል” የሚል ሲሆን ቀጥተኛ ትርጉሙም የኢትዮጵያ መንግስት ከፈቀደ ወይንም ከፈለገ በኢጣሊያ በኩል ከውጭ መንግስታት ጋር ግንኙነት ማድረግ እንደሚችል የሚጠቅስ ነው፡፡

የአንቀጹ የጣሊያንኛ ትርጉም ግን “የኢትዮጵያ መንግስት ከውጭ ሀገር መንግስታት ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት በኢጣሊያ መንግስት አማካኝነት ማድረግ ይገባዋል” የሚል ነበር፡፡

ይህም የኢትዮጵያን የውጭ ግንኙነት በቀጥታ በጣሊያን በኩል እንዲከናወን የሚያስገድድ ነበር፡፡

በአንቀጽ ፲፯ አማካኝነት ጣሊያን የውሉን ሀሳብ በጣሊያንኛ በመቀየር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት በመገርሰስ የጣልያን ሞግዚት እንድትሆን ቀዳዳ እያበጀች ነው ብለው ነገሥታቱ እና መኳንንቱ ስለተገነዘቡ የውጫሌ ውልን እንደማይቀበሉት አሳወቁ፡፡

የጣሊያን መንግስት ውሉን ለማፍረስ አሻፈረኝ በሚልበት ጊዜ፣ የውጫሌ ውል እንዲፈርስና ኢትዮጵያ ለማይቀረው ጦርነት እንድትዘጋጅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ግለሰቦች መካከል የዳግማዊ አጼ ምኒልክ ሚስት የሆኑት እቴጌ ጣይቱ ብጡል እንደነበሩ ታሪክ ይናገራል፡፡

እቴጌዋ “እኔ ሴት ነኝ፣ ጦርነት አልወድም፡፡ ግን እንዲህ መሳዩን ውል ከምቀበል ጦርነት እመርጣለሁ” ብለው ነበር፡፡ በወቅቱ “ይስሙ ንጉሥ!” የሚል ታሪካዊ ንግግር አድርገዋል፡፡ ይህን ንግግራቸውን ተከትሎም የውጫሌ ውል የተፈረመበት ቦታ “ይስማ ንጉሥ” በሚል ተሰይሞ እዚህ ዘመን ደርሷል፡፡

(more…)

Read Full Post »

የዝዋይ ገዳም ኮሌጅ የተመሠረተው ለማን ነው ?
———————————
( ሁሉም ሼር በማድረግ እውነቱን እንግለጥ )

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካሉ አምስት ኮሌጆች አንዱ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ ነው፡፡ ኮሌጆች ሲመሠረቱ ሀገር አቀፍና ዓለም ዓቀፍ ርዕይ ይዞ ነው:: የትኛውም ተቅዋም በቤተ ክርስቲያን ሲመሠረት ምዕመናንን ማዕከል (አድሬስ) ያደረገና የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ አምልኮትዋን ሳይዘነጋ ነው:: የዝዋይ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አጭር የታሪክ ዳሰሳ በሌላ ክታብ እንመለሳለን:: አሁን ግን ኮሌጁ እየሰጠ ያለውን ሰፊ አገልግሎት ለመጠቆም ነው:: የዝዋይ ገዳም በ1959 ዓ/ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የተመሠረተ ሲሆን በ1960 ዓ/ም ማስተማር ጀምሯል። በ1966 የመንግሥት ለውጥ ተከትሎ ተዘግቶ ቆይቷል::

በ1971 በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ አማካኝነት ዳግም ተከፍቷል:: ከዛን ጊዜ ጀምሮ በሺ የሚቆጠሩ መምህራንን ለቤተ ክርስቲያን አስረክቧል:: ገዳሙ ትንሿ ኢትዮጵያ ናት:: የገዳሙን ውሃ ጠጥቶ ስልጠናውን ወስዶ በሳል ሰባኪ ያልሆነ የለም:: በመላው ዓለም ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በማገልገል ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት ፡ ቆሞሳት ፡ ሰባክያነ ወንጌል ፡ ካህናት ዲያቆናት ምስክር ናቸው:: በዝዋይ ገዳም ዘር ቀለም የለም:: በዝዋይ ገዳም የሚያድጉ ወላጅ አጥ ሕፃናት ከሁሉም ቤተ እምነት መጥተው ነው የሚያድጉት:: ቀደምት የነበሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በአካለ ሥጋ የሌሉ በነፍሳቸው ምሥክር ናቸው:: በአካል ያሉ በበረከት ሕዝቡን እየጠበቁ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከአሥር በላይ ናቸው፡-

(more…)

Read Full Post »

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ!!

(የካቲት 16 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ)

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ኃላፊ በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው በማኅበራዊ የትሥሥር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት በቦረና እና አካባቢው በተከሰተው ድርቅ በርካታ ኢትዮጵያውያን በችግር ውስጥ እንደሚገኙ ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች ያመላክታሉ ያሉ ሲሆን የተከሰተው ድርቅ ወደ ረሀብ ተለውጦ ከዚህ በላይ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ሕይወት እንዳያልፍ መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፋቸውን ሊያደርጉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

መንግሥትም በአካባቢው ላሉ ወገኖች የሚያደርገውን ድጋፍ በማጠናከር የተቀናጀ የነፍስ አድን ተግባራትን በማከናወን ሊደግፋቸው ይገባል ሲሉም አክለዋል።

በመጨረሻም መላው ኢትዮጵያውያን በአካባቢው ለተከሰተው ድርቅ ትኩረት በመስጠት የወገኖቻችንን ሕይወት ለመታደግ ከጸሎት ጎን ለጎን የተቻላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አባታዊ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

Read Full Post »

አሁን አሁን ኦነጋውያኑ እነ ቀጄላ በተሰጣቸው ቦታ ሁሉ ለመተግበር የሚሞክሩት የውሸት ድሪቶ፤ መቼም ዓለም በሙሉ ዓደዋን ሲያስብ ያለ ንግሣችን ዳግማዊ ሚኒሊክ ማሰብ አይቻልም፤ ነገር ግን ኦነጋውያኑ ዳግማዊ ምኒሊክን ከዓደዋ በዓል አከባበር ወይም ፖስተሮች ላይ በሙሉ በማውጣት በምትኩ ከጉዳዩ ወይም ከክስተቱ ጋር ግንኙነት የሌለውን ዐብይ አሕመድን በፖስተር ላይ በመስቀል ታሪክን ሊቀይር ሊያሳስት እንዲሁም አዲስ ታሪክ በዓደዋ ሊጽፍ የዘንድሮውን ዓደዋ አከባበር ለሁለተኛ ጊዜ የውሸት ድሪቶውን ሲደርት ውሏል፤ ሲናገሩ ትንሽ እንኳን እማይሰቅቃቸው በጸጉራቸው ልክ የሚዋሹ የውሸት አባቶች የሆኑ የታሪክ አተላዎች ተሰባስበው፤ ሀርሩን የሚጠላ፣ የኢትዮጵያ ባለውለታ የሆኑትን የእምዪ ሚኒሊክን ታሪክ ሊቀብር ሊደብቅ በመውደቅ በመነሳት ላይ ይገኛል፤ ነገር ግን አይሳካም ፤ የእምዪ ሚኒሊክ ታሪክ በወርቅ ቀለም በብዙ ኢትዮጵያውያን ላይ ተጽፏል፤ ባንተ ድሪቶ ሊሰረዝ ወይም ሊቀየር የሚችል ነገር የለም፤

እነዚህ የታሪክ አተላዎች ዛሬ እነሱ የሚኮሩበትን የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በሙሉ ወደ ሃገራችን ያስገቡት ያሰለጠኑት እኚህ ታላቅ አፍሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ ንጉሥ ሆነው ሳለ ያንን ሁሉ በመካድ ከነ ስም አጠራራቸው ለማጥፋት እና ለመካድ ከመሪያቸው ከሃዲው ዐብይ ሳይቀር የሚኒሊክን ቤተመንግሥት “አንድነት ፓርክ” በማለት ስም አጠራሩን እንኳን እንዲካድ እንዲጠፋ እየሰራ ያለ የታሪክም የትውልድም ተጠያቂ ከሃዲያን መሆናችውን ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ እየታዘቡ እንደሆነ ልብ ይሏል ፤ ነገር ግን ዛሬ ላይ ዝም ስለተባልክ ከታሪክም ከሕግም ተጠያቂነት ማምለጥ እንደማትችል ልናረጋግጥልህ እንወዳለን።

(more…)

Read Full Post »

Older Posts »