Feeds:
Posts
Comments

Archive for July, 2013

 

  • ኮሌጁ እንዲዘ የውሳኔ መነሻ የሰጠው ከአቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ያልወጣው የኮሌጁ ቦርድ ነው
  • የኮሌጁ ምግብ ቤት አገልግሎቱን እንዲያቆም በመታዘዙ ደቀ መዛሙርቱ ምሳና ራት ተከልክለው ውለዋል
  • አቤቱታቸውን ለመንግሥት አካላት ያሰሙት ደቀ መዛሙርቱ ‹‹ቅ/ሲኖዶስ እና ምእመናን የከፈቱት ኮሌጁ የሚዘጋው በመቃብራችን ላይ ነው!›› በሚለው አቋማቸው ጸንተዋል፤ በአስተዳደር ሕንጻው ዙሪያ የሚያደርጉትን ቁጥጥር አጠናክረዋል

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት ኮሌጁን ለቀው እንዲወጡ ለማስገደድ የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት የፌዴራል ፖሊስ ኀይልን እገዛ መጠየቁ ተገለጸ፡፡

በልዩ ጽ/ቤቱ የበላይ ሓላፊ ብፁዕ አቡነ ገሪማ ስም ተፈርሞ የወጣውና ለፌዴራል ፖሊስ እንደተጻፈ በተገለጸው ደብዳቤ÷ ልዩ ጽ/ቤቱ የኮሌጁን ደቀ መዛሙርት በሰላም ነሽነት በመወንጀል ኮሌጁ እንዲዘጋ መወሰኑን ያስታወቀ ሲኾን በዚህም መሠረት ፖሊስ ደቀ መዛሙርቱ ኮሌጁን ለቀው የሚወጡበትን ርምጃ እንዲወስድ እገዛ መጠየቁ ታውቋል፡፡

የልዩ ጽ/ቤቱ ደብዳቤ የተጻፈው በኮሌጁ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ተጽዕኖ ውስጥ እንዳለ የሚነገረውና በደቀ መዛሙርቱ የችግሩ አካል ተደርጎ የሚተቸው የኮሌጁ ቦርድ ኮሌጁ እንዲዘጋ በሰጠው የውሳኔ መነሻ መኾኑ ተነግሯል፡፡

(more…)

Read Full Post »

Board members of the college

  • ፖሊስ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ዋና ሥራ አስኪያጅ አነጋግሯ
  • ‹‹ከሣሾቼን እንዳታነጋግሩ›› ያሉት አቡነ ጢሞቴዎስ ቋሚ ሲኖዶሱ በጉዳዩ ላይ እንዳይወያይ ማከላከላቸው ተሰምቷል
  • በተቃውሞው የተበሳጩት ሊቀ ጳጳሱ ራሳቸውን ስተው እንደነበር ተጠቁሟል
  • ‹‹አልፈው በመቃብራቸው ላይ መሣቅ እንፈልጋለን›› – የጥላቻው ምሬት
  • ‹‹በተራዘመው መርሐ ግብር ሳቢያ የተጨመረው በጀት ለብክነት እየተዳረገ ነው›› /ደቀ መዛሙርቱ/

ዛሬ ጠዋት ወደ መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ያመሩት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽር ላይ የተቃውሞ ትዕይንት እያካሄዱ ነው፡፡

ጥቁር የአገልግሎት ቀሚሳቸውንና መጽሐፍ ቅዱስ በመያዝ ወደ መንበረ ፓትርያሪኩ በሰልፍ ያመሩት ደቀ መዛሙርቱ፣ ወደ ቅጽሩ እንዳይዘልቁ በጥበቃ ሓላፊው በታገዱበት ነው የተቃውሞ ትዕይንታቸውን በማካሄድ ላይ ያሉት፡፡

ወደ መንበረ ፓትርያሪኩ ለመግባት የተፈቀደላቸው የደቀ መዛሙርቱ መማክርት መሪዎች/ተወካዮች ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ሓላፊዎች ጋራ እየተነጋገሩ እንዳሉ የተመለከተ ሲኾን ቋሚ ሲኖዶሱም በጉዳዩ ላይ እየመከረበት ስለመኾኑ፣ ‹‹በግቢው ጥበቃ ሓላፊ አቶ ብርሃኔ ኀይሉ ተነግሮናል፤›› ብለዋል፡፡

(more…)

Read Full Post »

ያለበደላቸው ግፍ እየደረሰባቸው ያሉት አባቶቻችን ረደኤት በረከት ይደርብን አሜን

ያለበደላቸው ግፍ እየደረሰባቸው ያሉት አባቶቻችን ረደኤት በረከት ይደርብን አሜን

ገዳማውያኑ ያለበደላቸው ለምን ይንገላቱ?

ከትናንት በስቲያ በደረሰን ሪፖርት እንደሚያመለክተው ላለፉት ጥቂት ወራቶች ሲደረግ እንደነበረው ታጣቂዎች በመነኮሳቱ ላይ ድብደባ፣ እንግልት፣ ስድብ እና እስራት እየፈጸሙባቸው ይገኛሉ። መንግሥት በዋልድባ ገዳም ላይ የሥኳር ፋብሪካ፣ የወርቅ ማዕድን ማውጫ፣ የፖርክ ይዞታን እከልላለው ብሎ በመነሳት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካሏት በርካታ ገዳማት በጥንታዊነቱ እና በታሪካዊነቱ የሚታወቀውን የዋልድባ (ዋሊ) ገዳም ለማፍረስ እና ገዳማውያኑን ለማሰደድ አረማውያን ደፋ ቀና ማለት ከጀመሩ ውለው አድረዋል። ይህ ሁሉ ግፍ እና በደል በገዳማውያኑ ላይ ሲደርስ በሰዎች ዘንድ ምንም ጥያቄ እና የመከላከል እርምጃ ባይደረግም ነገር ግን የቤተክርስቲያኒቱ መስራች መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተለያየ ጊዜ የተለያየ ተዓምራትን እያሳየ በርካታ እንቅፋቶችን ቢፈጥርባቸውም፥ ነገርግን በእምቢተኛነት ተግዳሮቱን እንደቀጠለ ነው፥ ነገር ግን የልብሳቸውን አዳፋነት፣ የሰውነታቸውን ክሳት አይቶ ሳይፈራ ስቃይንና መከራን ያበዛባቸውን አረማዊ እንዳይፈሩ በትንቢተ ኢሳያስ ፶፩ ፥ ፯ ላይ የሰፈረውን ቃል መመልከት በቂ ነው፤ እንዲህ ይላል “ጽድቅን የምታውቁ ሕጌም በልባችሁ ያለ ሕዝብ ሆይ፥ ስሙኝ የሰውን ተግዳሮት አትፍሩ፥ በስድባቸውም አትደንግጡ።” ኢሳ. ፶፩ ፥ ፯

Read Full Post »

ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከያዮች አንድነት (ዋልድባን እንታደግ) በሜሪላንድ ዩኒቨርሲቲ በርድ ስታዲዮም በሚደረገው የሰሜን አሜሪካ የስፖርትና የባሕር ፌዴሬሽን 30ኛ ዓመት በዓል ላይ በመገኘት በዓሉ ላይ ለመገኘት ለሚመጡት ኢትዮጵያውያን ግንዛቤት በማስጨበጥ እና ተቋሙን ለማጠናከር የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በመሥራት ላይ ይገኛል። ይህ በዓል በኢትዮጵያውያን ዘመን አቆጣጠር ከሰኔ ፳፭ ቀን ጀምሮ እስከ ሰኔ ፳፱ ቀን ፳፻፭ ዓም (June 30 – July 6, 2013) የሚቀጥል ሲሆን በበዓሉም ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከመላው ዓለም የሚገኙበት ሲሆን ምዕመናን፣ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ልጆች፣ የቤተክርስቲያኒቷ ወዳጆች በርካታ እርዳታዎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል እያበረከቱም ነው ለዚህም አምላከ ቅዱሳን ዘወትር የማያልቅበትን በረከቱን ለምዕማናን እንዲያበዛልን እየተመኘን በሚቀጥሉት ሦስት ቀናትም ዝግጅቱ ስለሚቀጥል በዓለም ዙሪያ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በትብብራችሁ እንትበረቱ እና ቅድስት ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ከጥፋት፣ ገዳማት አድባራቱን ከምዝበራ፣ ንጹሐን መነኮሳትና መነኮሳይትን ከስደት፣ ዋልድባን ከመፈታት እንድንታደግ አደራ እንላለን።

በዚህ በዓል ላይ እጅግ በሚያኮራ እና በሚያስደስት ፍፁም የቤተክርስቲያን ቅንዓት ጫማዎችን በመጥረግ (ሊስትሮ)

 

DSC_2551 DSC_2566 DSC_2569 DSC_2571 DSC_2574 DSC_2577 DSC_2583

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

በማስጠረግ በርካታ ክርስቲያኖች ትብራቸውን እያደረጉ ነው በዚህም ቤተክርስያናቸውን ከጥፋት ለመታደግ፣ ዋልድባን እና የተለያዩ ገዳማትን ለመታደግ በሚደረገው እንቅስቃሴ ተባባሪነታቸው አሳይተዋል እና በመጨረሻው ዘመን አምላከ ቅዱሳን በክብር በሚገለጽበት ጊዜ “ኑ እናንተ የአባቴ ቡሩካን” ተብለው ከሚጠሩት ከቅዱሳን ወገን እንዲደምርልን ለአምላካችን ዘወትር በጸሎት እናመለክታለን።

 

 

 

በድንኳን 41 ፊትለፊት ይደረጋል ከ4:00 PM. ጀምሮ

በድንኳን 41 ፊትለፊት ይደረጋል
ከ4:00 PM. ጀምሮ

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

በመጨረሻ በበዓሉ መጨረሻ ላይ ማለትም አርብ ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. (July 5, 2013)  4:00 PM. ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ፈተናዎች እና የመንግሥት ተግዳሮት በሚል ርዕስ ዝግጅት ስለሚኖረን በድንኳን ቁጥር 41 ፊትለፊት በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ በታላቅ አክብሮት ተጋብዘዋል።

 

Let’s save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!

Read Full Post »