- ለመነኰሳቱ የአስቸኳይ ጊዜ የምግብና የአልባሳት እርዳታ ጥሪ ቀርቧል
(አንድ አድርገን ህዳር 10 2005 ዓ.ም)፡– በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ዓዲ አርቃይ ወረዳ የሚገኘው
የጥንታዊው ዋልድባ ደልሽሐ ኪዳነ ምሕረት ማኅበረ ደናግል ገዳም ሴት መነኰሳት ኳሬዳ በተሰኘ ትልናበአካባቢው
በብዛት በሚፈላው ምስጥ መቸገራቸውን ለገዳሙ የራስ አገዝ ልማት ርዳታ ለማሰባሰብየተቋቋመው ኮሚቴ ገለጸ፡፡
ትሉ መነኰሳቱ ለዘመናት የኖሩባቸውን ጎጆ ቤቶች /የሣር መክደኛ/ ምቹመራቢያ እንዳደረገው የተገለጸ ሲሆን
ትሉን በምትገበው ኩቱ የተባለች ወፍ በሚራገፍበት ወቅትበመነኰሳቱ ቆዳ ላይ እያረፈ ሰውነታቸውን ያሳብጣል፤
ዕብጠቱ ከሚፈጥረው ሥቃይ ለመዳን መነኰሳቱሰውነታቸውን በምላጭ ስለሚበጡት ተጨማሪ ጉዳት
እያስከተለባቸው ነው፡፡ በአካባቢው በብዛትየሚፈላው ምስጥ ሌላው የማኅበረ ደናግሉ ፈተና መኾኑ ሲሆን
አረጋውያትና ሕሙማን መነኰሳትየሚረዱባቸውን የአልጋ ቆጦችና የቤት ቋሚዎች እየቦረቦረ በመጣል ለጉዳት
እየዳረጋቸው መኾኑ ታውቋል፡፡
ኳሬዳ ለተሰኘው ትል በምቹ መራቢያነት የተጠቀሰውን የሣር ጎጆ በቆርቆሮ ክዳን በመለወጥ ለመከላከል
እንደሚቻል በተሞክሮ የተረጋገጠ ሲሆን ቤቶቹ የተደገፉባቸውን የዕንጨት ምሰሶዎች በግንብ /ኮንክሪት/
በመተካት ደግሞ የምስጡን ጥቃት መቋቋም የሚቻል በመኾኑ በጎ አድራጊ ግለሰቦችና ድርጅቶች በሀገረ
ስብከቱ ጥያቄና በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ፈቃድ ከተቋቋመው የገዳሙ እርዳታ አሰባሳቢና ልማት ኮሚቴ
ጋራየተጠየቁትን የግንባታ ቁሳቁሶች በዐይነትና በገንዘብ በመስጠት የተቻላቸውን እገዛ እንዲያደርጉ የኮሚቴው
ሓላፊዎች ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
በቁጥር ከሦስት መቶ ኀምሳ ያላነሱ ሴት መነኰሳዪያት ብቻ በማኅበር ለሚኖሩበት ገዳም የእህል ወፍጮ፣
የውኃ መሳቢያ ሞተርና የውኃ ማጠራቀሚያ ታንኮችን ለመትከል፣ ዘመናዊ የንብ ማነብ/የማር ምርት/
እናሌሎችም የራስ አገዝ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር እንደሚንቀሳቀስ የጠቆመው ኮሚቴው አክሎ
እንደገለጸው÷ እንደ ጾሙና ጸሎቱ ሁሉ ሥራን የጽድቅ መሠረት አድርገው በማኅበር የሚኖሩት ከሦስት
መቶ ኀምሳ በላይ ማኅበረ ደናግሉ፤ በከፍተኛ ሙቀትና በሌሎችም የአካባቢ ለውጦች ሳቢያ ራሳቸውን የሚረዱባቸው
የዳጉሳና የማሽላ ሰብሎቻቸው ፍሬ ሊሰጧቸው ስላልቻሉ አስቸኳይ የምግብ (ባቄላ፣ዘንጋዳ፣ ዳጒሳ፣ ሰሊጥ፣
ኑግ፣ ጨው፣ በርበሬ) እና የአልባሳት (ስድሳ ጣቃ አቡጀዲ ጨርቅ) እርዳታእንደሚያስፈልጋቸውም አስታውቋል፡፡
ምንጭ ፡- አዲስ አድማስ ጋዜጣ
Leave a comment