Feeds:
Posts
Comments

ገዳመ ዋልድባ ላለፉት 1600 ዓመታት ተከብሮ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ እኛ ላይ ደርሶ ነበር። በአሁን ሰዓት መንግሥት በልማት ሰበብ ሸንኮራ አለማለሁ፣ እምነበረድ ፋብሪካ አቋቁማለሁ፣ የወርቅ ማዕድን ማውጫ እሰራለሁ፣ ወዘተ በማለት ልማት እያለ ታላቁን፣ ታሪካዊውን የኢትዮጵያ ሃብት ለማጥፋት ብሎም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካሕናት፣ ዲያቆናት፣ መነኮሳት፣ ቆሞሳት እና ጳጳሳት ምንጭ የሆነውን ገዳም ለማድረቅ እና ለማጥፋት ወገቡን ታጥቆ ከተነሳ ሰንበት ብሏል። ኢትዮጵያውያንም ለሃይማኖት የማይቆረቆር ግዴለሽ ትውልድ ሆኗል እና ዛሬ የመፍረስ እና የመበተን ፍርድ የተፈረደበት ገዳም ገዳማውያን ያለጥፋታቸው እየታሰሩ፣ እየተደበደቡ፣ እንደወንጀለኛ ያለፍርድ በየእስር ቤቱ እየታጎሩ ይገኛሉ፣ ታዲያ ማነው ለምን ብሎ ሊጠይቅ የሚገባው እኛ አይደለንም እንዴ አንዱ በሬዲዮ “ገዳሙን አንነካም ብለዋል” ይለናል እነሱማ ሁሉንም ይላሉ አረማውያን ጸሐፍት ፈሪሳውያን ጌታን ሲሰቅሉት እኮ ምክንያት አበጅተው ነው ሕይወት የሚሆናቸውን ሰቀሉት ዛሬም የኛ ሰው ለመጪው ትውልድ ታሪክ ማጣቀሻ የሚሆነውን ብርቅ እና ድንቅ ገዳም ለማፍረስ ደፋ ቀና ይላሉ እውን እነዚህ ለኢትዮጵያ አሳቢዎች ናቸው?? ትልቅ ጥያቄ ነው ዛሬ ታሪኮቻችንን ቅርሶቻችንን እና ብርቅና ድንቅ የሃገራችንን ሃብቶች ቀስ በቀስ እያጣናቸው ነው ማን ይጠይቅ?
ትላንት የአቡነ ጴጥሮስን ሃውልት አፈረሱ እውን እቦታው ይመለስ ይሆን? ሁላችንም የምንመለከው እውነታ ነው
የሉሲ ቅሪት በጉብኝት ሰበብ በብዙ ሚሊዮን ብሮች ወጥታለች ትመለስ ይሆን?
እድሜ ጠገብ የሆኑት የብራና መጻሕፍት የወርቅና የብር መስቀሎች ከየገዳማቱ እየተዘረፉ ለገባያ ውለዋል ማን ይጠይቅ
ልብ ያለው ልብ ይበል

Let’s save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!

አቶ አባይ ጸሀይ በአባ ወልደ ማርያም አማካኝነት ከዋልድባ መነኮሳት ጋር ተነጋገሩ

  • መናኝ ኃይለመለኮት ከእስር ተፈቱ፥ ነገር ግን በአስቸኳይ ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ተነገራቸው
  • ከትንሳኤ በኃላ ከገዳሙ የሚባረሩ እንደሚኖሩም ተጠቁሟል
  • ማቄን ጨርቄን ሳትሉ ቦታውን ጥላችሁ ውጡልን

 በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ 

ባለፈው አርብ እለት ማታ በተከሰተው በታጣቂዎች በማይለበጣ እናበዳንዶሮቃ ዘረፋ ከተፈጸመ በኃላ በቀጣዩ እለት ማለትም ቅዳሜ መናኝ ኃይለመለኮት የተባሉትን አባት ያለ ጥፋታቸው ወደ ማይጸብሪ በመውሰድ በእስር ላይ እንደነበሩ ይታወሳል። በእለቱ አሉ ተብለው ለእስር የዳረጋቸውም “ታጣቂዎች ይዘርፉናል፥ ታጣቂዎች የዳኙናል” በሚል ሰበብ እንደነበረ ዘግበን እንደነበረ ይታወሳል። በዚሁ እለትም በታጣቂዎች ተደብድበው የሕክምና እድል እንኳን ማግኘት ያልቻሉትንም አባ ፍቅረማርያምን እስከ አሁን ድረስ ደማቸውን ከሚጠራርጉላቸው ወንድሞቻቸው በቀር የረባ ሕክምና ወደ ማይጋባ ወስደን እናሳክም ብለው የጠየቁትን “አይመለከታችሁም አርፋችሁ ተቀመጡ” በማለት ማስፈራራት ደርሶባቸዋል፥ እኝህ አባትም እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ምንም አይነት ህክምና ሳያገኙ መቆየታቸውን ስጋታቸው አባቶች ገለጸውልናል፥ ነገር ግን ከሰዎቹ ፈቃድ ውጪ ምንም ለማድረግ አለመቻላቸውም በእጅጉ አሳዝኗቸዋል።

 

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፈው ቅዳሜ የታሰሩት መናኝ ኃይለመለኮት ከታሰሩበት እስር ቤት ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው ወጥተዋል። በትዕዛዙ መሰረትም መናኝ ኃይለመለኮት ወደ ገዳሙ የመግባት ፈቃድ እንደሌላቸው እና በቀጥታ ወደሚሄዱበት እንዲሄዱ አሳሪዎቻቸው አስፈራርተው ነግረዋቸዋል። ከጥቂት ወራት በፊት ወደ አርባ የሚጠጉ አባቶች እና እናቶች የሚደርስባቸውን በደል በባሕርዳር ለአማራ ክልል ፕሬዘዳንት ቢሮ፣ ለክልሉ የጸጥታ ክፍል፣ ለክልሉ የፓሊስ ኮሚሽነር ቢሮ፣ በጎንደር ከተማ ለሚገኙት ለሰሜን ጎንደር ሃገረ ስብከት ጽ/ቤት፣ ለሰሜን ጎንደር የጸጥታ ቢሮ አቤቱታቸውን እንዳሰሙ ይታወሳል፥ በመጨረሻም የሰሜን ጎንደር ሃገረ ስብከት ጸሐፊ፣ የሰሜን ጎንደር የጸጥታ ክፍል ሃላፊዎች ከማይጸብሪ አስተዳዳሪ ጋር በመነጋገር ችግራችሁን እዛው ሄደን ተነጋግረን እንፈታዋለን ተብለው ሳይፈልጉ በግድ ከጎንደር ተግዘው (ተገደው) ማይጸብሪ ተወስደው የስድብ እና ማንጓጠጥ መዓት ወርዶባቸው ወደ ገዳማቸው እንደገቡ ይታወሳል። ከገቡም በኃላ በየእለቱ ተደጋጋሚ ማስፈራሪያ ደርሶባቸው የበረቱት በውድቅት ሌሊት ሕይወታቸውን ለማቆየት ከገዳሙ ተሰደው በተለያዩ የክልሉ ገዳማት ገብተው እንዳሉ ለመረዳት ችለናል። ቅዳሜ እለት ለእስር የተዳረጉት መናይ ኃይለመለኮትም በወቅቱ ማስፈራራት ከደረሳቸው አባቶች መካከል አንደኛው ሲሆኑ፣ የሚመጣውን እንደጌታዬ እየሱስ ክርስቶስ በጸጋ እቀበለዋለሁ ብለው በገዳሙ ቆይተው እንደነበር የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በዚህም ምክንያት ሳይሆን እንደማይቀር አንዳንድ አባቶች ይገምታሉ መናኝ ኃይለመለኮትን ለእስር ያበቃቸው እንጂ ከሳሾቻቸው (ታጣቂዎቹ) እንደሚሉት “ታጣቂዎች ዘረፉን፥ ታጣቂዎች ይዳኙናል” የሚለውን ቃል እሳቸው እንዳልተናገሩ ለመረዳት ችለናል።

Continue Reading »

በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለዘመናት እየተንከባለለ የመጣው ችግር ዛሬም ለመመረቅ ጥቂት ወራት የቀራቸውን ደቀ መዛሙርት ተስፋ በሚያስቆርጥ መልኩ ከቅዱስ ፓትሪያርኩ ጀምሮ እስከ ኮሌጁ የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ጢሞቲዎስን ጨምሮ ሁለት መምህራን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ትምህርት አያስተምሩም፣ ችግር አለባቸው ቢባሉም እኛ ያልነው ብቻ ልክ ነው በሚል፣ ይልቁንም ሌላ ተልዕኮ አላችሁ፣ የቀደመ የቤተክርስቲያን ትምህርት የላቸውም እና የመሳሰለውን ምክንያት በመስጠት ችግሮችን ከመፍታት ይልቅ ምክንያት መደርደር የሚወዱት የኮሌጁ የቦርድ አባላት እና የበላይ ጠባቂው ኮሌጅን ያህል የቤተክርስቲያኒቱን ትልቅ ተቋም እንደግል ቢሮአቸው በሰረገላ ቁልፍ ክርችም ካደረጉት ወራት ተቆጥረዋል። የደቀ መዛሙርቱን ችግር ለማዳመጥ ጆሮውን የሰጠ የኮሌጁ ዲን የለም፣ የበላይ ጠባቂውም በችግሩ ላይ ችግርን ጨምረው፣ የሚመለከተው ቅዱስ ሲኖዶስም ዝም ብሏል፣ ምዕመናንም ዝም ብለዋል፣ ሁሉም ዝም ብለዋል በመካከሉ ግን ስውር ዓላማ ያላቸው ቤተክርስቲያኒቱን ወደ ሌላ ተቋም ለመቀየር የሚጣጣሩት አካላት ተሳክቶላቸዋል፡፡ ነገ እነዚህ ደቀ መዛሙርት ተመርቀው ወጥተው ወልድ ዋሕድ ብለው የሚያጠምቁ፣ የቅድስት ቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ይዘው ዓለምን በወንጌል ሊያዳርሱ የሚችሉ በሁለት ሰዎች ምክንያት ከ5000 በላይ የሚሆኑ ደቀመዛሙርት ለረሃብ፣ ለጥም፣ እና ለዕርዛት ተዳርገዋል። ኸረ የቤተክርስቲያን አምላክ በማለት ጩኸታቸውን እያሰሙ ባሉበት ወቅት የVOAው ዘጋቢ አቶ አዲሱ አበበ ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ቀደምት ተማሪ እና መምህራን ከነበሩ እንዲሁም በአሁን ሰዓት ችግር አለብን ብለው የሚጠይቁትን የደቀመዛሙርቱን ተወካይ እንግዶችን አነጋግሯል ከነዚህም መካከል 

  Continue Reading »

  • ማይለበጣ ቤተ-እግዚአብሔር በታጣቂዎች ተዘረፈ
  • ·         ዶንዶሮቃ ላይ የሚገኘው የዋልድባ ገዳም ወፍጮ ቤትም በተመሳሳይ ታጣቂዎች ተዘርፏል
  • አባ ፍቅረማርያም የተባሉ አባት በደረሰባቸው ከባድ ድብደባ በህክምና ላይ ናቸው
  • መናኝ ገብረመድኅን የተባሉ ስመ እግዚአብሔር ጠርተው ለምነው ከድብደባ ድነዋል
  • መናኝ ኅይለመለኮት የተባሉ አባት “ታጣቂዎች ዘረፉን፣ ደበደቡን፥ ታጣቂዎችም ሊዳኙን መጡ” ብለዋል በሚል ወደ እስር ቤት ተጥለዋል

 

እለቱ አርብ ሚያዚያ ፲፩ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. ማታ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ሲሆን ጭልም ድቅድቅ በሆነበት ሰዓት ላይ ማይለበጣ በሚገኘው ቤተ እግዚአብሔር ላይ በከባድ የሚሊተሪ ልብስ እና ትጥቅ የታጠቁ በግምት ስድስት የሚሆኑ ታጣቂዎች በውጪ በረንዳ ላይ ተኝተው የነበሩትን መነኮሳት እና መናንያን ደብድበው እና ብዙ እንግልት አድርሰውባቸው ገንዘብ ያለው የት ነው ተናገሩ በሚል ብዙ እንግልት እና ድብደባ እንዳደረሱባቸው ከቦታው በደረሰን መረጃ መመልከት ችለናል። በመጨረሻም ታጣቂዎቹ ከመሄዳቸው በፊት ጽ/ቤቱን በሰደፍ ሰብረው ሲያበቁ በጽ/ቤት ውስጥ ያለውን ንብረት በመወርወር ሲያምሱ ቆይተው ምንም ባለማግኘታቸው ተበሳጭተው መነኮሳቱን ደብደበው እና አንገላተው ጥለው ወጥተው ለመሄድ ችለዋል።

Continue Reading »

  • የአዲርቃይ ፍርድ ቤት ገዳማችን አይታረስም በማለታቸው ወጣቶችን በአሸባሪነት ከሰሰ
  • በዛሬማ የሚገኙ ነዋሪዎች በወጣቶቹ ላይ ምስክርነት አንሰጥም በማለታቸው እንግልት እየደረሰባቸው ነው
  • የሰሜን ጎንደር ጸጥታ ክፍል ክሱ በአሸባሪነት መሆን አለበት በማለት ትዕዛዝ አስተላልፏል
  • የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከገዳሙ በረከት ለመቀበል የመጡት ማስፈራሪያ እና ፍተሻ (strip search) ተደረገባቸው
  • የጣሊያኑ ኮንስትራክሽን ሌላ አማራጮችን እንፈልግ ብሏል
  • የወልቃይት ነዋሪም እርሻውን እንዲቀጥል እስከሚመጣው ዓመት ምንም ነገር እንደማይኖር እየተነገረው ነው

ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ 

ethiopian-sugar-corporation-projects-map

የዛሬ ዓመት አካባቢ ይሆናል የዛሬማ ወጣቶች ከመንግሥት ጋር ገዳማችን አይታረስም፣ የአባቶቻችንን ድንበር አናስነካም በማለት ከመንግሥት ታጣቂዎች ጋር ግብግብ የተፈጠረው፥ በወቅቱ የክልሉ ባለሥልጣናት በቦታው ተገኝተው ከዛሬማ ነዋሪዎች ጋር ስብሰባ አድርገው የዛሬማን ነዋሪ ውሳኔ እንዲሰጥ እያስፈራሩ ባሉበት ወቅት ነበር ጥቂት ወጣቶች የአባቶቻችንን ድንበር አናስነካም፣ ገዳማችንንም ፈቅደን አናሳርስም በማለታቸው ጥቂቶቹን በወቅቱ ወደ እስር ቤት ሲከቷቸው የተቀሩት አምልጠው ጫካ ገብተው ገዳማችንን ማንም ሊነካውም፣ ሊደፍረው፣ ሊረግጠውም አይገባም በማለት ጥሪያቸውን ሲያቀርቡ ቆይተዋል የአካባቢውንም ገበሬ ማኅበራት፣ የሃገር ሽማግሌዎችን በማነጋገር እንዴት ዓይናችን እያየ ገዳማችንን የማንም አማቄላውያን (አረማውያን) መፈንጫ ይሆናል፣ ይሄ ቦታ እኮ የቅዱሳን ማረፊያ፣ የግዑሳን መጠጊያ ለእኛ ለተዳደፍነው እረፍት፣ በረከት፣ ቅድስና ለማግኘት የምንሄድበት እንጂ እንዴት እነዜህ አረማውያን ዛሬ እንደፈለጉት ያደርጉታል በማለት ተቃውሟቸውን በከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ከሃገረ ስብከቱ ሃላፊዎች ቢያቀርቡም የተወሰኑ የመንግሥት ሃላፊዎች በሃገር ሽማግሌዎች ምከሯቸው እና ወደ ቤታቸው እና ቤተሰባቸው ይመለሱ በማለት አግባብተው ወደ ሃገራቸው እና ቤተሰባቸው ከተቀላቀሉ የሦስት ወይም ሁለት ወር አይበልጣቸውም ነበር።

 

የኢትዮጵያ መንግሥት ሊያስገነባቸው ያሰባቸው የስኳር ፋብሪካዎች

ወጣቶቹም ወደ ሃገራቸው እና ወደ ቤተሰቦቻቸው እንደተመለሱ ብዙም ሳይቆይ የአዲርቃይ ከተማ አቃቤ ሕግ ቢሮ ደብዳቤ ከሰሜን ጎንደር የጸጥታው ቢሮ ይደርሰዋል በደብዳቤውም ላይ “ከዚህ በፊት ታስረስው እና በምሕረት የተመለሱት ወጣቶች በሙሉ በአሸባሪነት፣ በመንግሥት ላይ በመነሳት፣ እና ከግንቦት 7 ታጣቂዎች ጋር በመተባበር” በአስቸኳይ እንዲከሰሱ እና የፍርዱንም ሄደት እንደሚከታተሉት ጠቅሰው ደብዳቤ ይጽፋሉ። ደብዳቤ የደረሳቸው የአቃቢ ሕጉ ቤሮ ሰራተኞች ወደ ዛሬማ በመሄደ ከከተማው የመንግሥት ተወካዮች እና የጸጥታው ሃላፊዎች ጋር መመካከር ይጀምራሉ፥ የዛሬማ ከተማ መስተዳደር እና የጸጥታው ሃላፊዎች እንዴት ብለን ነው በአሸባሪነት የምንከሳቸው? በምን መረጃ ነው ብለው ሲጠይቁ ሰዎችን አስመስክሩባቸው በማለት የአቃቢ ሕጉ ሰራተኞች ቢጠይቁም ጥቂት የአካባቢው ነዋሪዎች ተጠርተው የምስክርነት ቃላቸውን እነሱ በሚፈልጉት መልኩ ከመሰከቱ ወሮታውን መንግሥት እንደሚሰጣቸው ቢያብሏቸውም “እኛ በልጆቻችን ላይ የሃሰት ምስክር ልንሆን አንችልም፣ የምናውቀው ነገር ቢኖር ገዳማችንን አትንኩ ማለታቸውን ነው በማለት እንቢታቸውን ገልጸዋል” የአካባቢው ነዋሪዎችም እንሰዛሬ ድረስ ሰዎችን እንዲህ እየደረጉ ነው ለካ በሃሰት እየከሰሱ ያሉት እነኝህ ወጣቶች ያደረጉት ነገር ቢኖር ገዳማችን አትንኩ ከማለት በስተቀር እንኳን አሸባሪ ሊሆኑ ጭራሽ እንዴት እንዲህ ዓይነት ክስ ሊመሰርትባቸው ይችላል በማለት ቅሬታቸውን ደጋግመው በማሰማት የአካባቢው የጸጥታ ቢሮ እና የአዲርቃይ የአቃቢ ሕግ ሰራተኞች ተመካክረው ወጣቶቹን በአሸባሪነት ቀርቶ በሌላ ክስ ሊመሰርቱባቸው ተስማምተው ነበር ጉዳዩ

Continue Reading »

·       “የትግራይ ክልል ተወላጅ ካልሆናችሁ በዚህ ገዳም መኖር አትችሉም” ተብለናል፤

·       “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዋልድባ የሚለውን ስም መጥራት ሁሉ የተለየ ይዘት እየተሰጠው” ነው፤
  •       መነኮሳት ይታሰራሉ፤ ይደበደባሉ፤
  • ከክልሉ ፕሬዚዳንት ጋር ተነጋግረዋል ተብሏል።
(ደጀ ሰላም፤ ጥር 12/2005 ዓ.ም፤ ጃኑዋሪ 20/2013/ PDF)፦ የዋልድባ የዋልድባ አብረንታንት ገዳም ቤተ-ሚናስ ማኅበረ መነኮሳት አቤቱታቸውን ለአማራ ብሐየራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት እና ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አቀረቡ። በመነኮሳት ላይ የሚደርሰውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ የዘረዘረው ደብዳቤው የክልሉ መንግሥት በሰላማውያን መነኮሳት ላይ የሚደርሰውን እንግልት እንዲያስቆም ጠይቀዋል። የታሰሩ፣ የተንገላቱ፣ ሰብዓዊ መብት ጥሰት የደረሰባቸውን መነኮሳትም ዝርዝር አቅርበዋል። ሙሉ የደብዳቤው ሐሳብ ቀጥሎ ሰፍሯል።

የክልሉ መንግሥት የመናንያኑን አቤቱታ ይቀበል ይሆን? የምናየው ይሆናል።

ቸር ወሬ ያሰማን አሜን
አንድ አድርገን (ጥር 05 -2005)፡- መንግሥት በዋልድባ አካባቢ እገነባዋለሁ የሚለውን የስኳር ፕሮጀክት ከጀመረ ወራት ተቆጥረዋል ፡፡ አንድ ጊዜ በጸባይ ሌላ ጊዜ ደግሞ በፈርኦናዊው ጡንቻው በማስፈራራት አላማውን ከግብ ለማድረስ ብዙ እየሞከረ ይገኛል ፡፡ መነኮሳቱን በጎጥና በቋንቋ እንዲከፋፈሉ ሁለትም ሃሳብ እንዲሆኑ ብዙ ጥሯል ፤ ዋልድባ ገዳም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ታላቅ ገዳም መሆኑን ወደ ኋላ በማለት ቦታውን የትግራይ ክልላዊ መንግስት አካል እንጂ የአማራ ክልላዊ መንግስት አይደለም ስለዚህ በገዳሙ ላይ ሃሳብ መስጠት የሚችሉት የክልሉ ተወላጅ የሆኑት መነኮሳት እንጂ ማንም አይደለም የሚል ሃሳብ በማንሳት ጉዳዩን ወደ ሌላ መንገድ ለመውሰድ ተሞክሯል ፤  በየጊዜው በቦታው ላይ የሚካሄደው ነገር ለመገናኛ ብዙሃን በማሳወቅ ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ የሚገኙትን አባት እሳቸውን ለጠቆመ የኮንዶሚኒየም ቤት እና ብዙ ሺህ ብር እንደሚሰጠው መንግሥት ለአካባቢው ነዋሪዎች ሲገልጽ ተስተውሏል ፤ ግንባታውን የጀመሩት አንድ ሀገር በቀል እና አንድ አለም አቀፍ ተቋማት ስራውን በተለያዩ ምክንያቶች መስራት ተስኗቸው በአሁኑ ወቅት ሶስተኛ አለም አቀፍ ኮንትራክተር ወደ ቦታው ለሁለቱ ያልተሳካውን ሊሞክር ስራውን ጀምሯል ፡፡ የሥኳር ኮርፖሬሽን ኃላፊ አቶ አባይ ጸሃዬ ለኢቲቪ እንደተናገሩት ከሆነ ሶስተኛው ኮንትራክተር ስራውን ከመጀመሩ በፊት በዛሬማ አካባቢ የሚሰራው ግድብ ጥቂት በሚያሰራ መልኩ ማስተካከያ እንደታከለበት ጠቁመዋል፡፡ የቦታውን ሁኔታ ለቪኦኤ የገለጹት መነኩሴ እንዳሉት አዲስ የገባው ኮንትራክተር የጣሊያል ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ “መነኮሳቱ ከአካባቢው ካለቀቁ ስራውን ለመስራት እንቸገራለን” እንዳሉ ገልጸዋል፡፡

Continue Reading »

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

አደባባይ

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

ስንክሳር (Senksar)

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

ቀዳሚ ገጽ

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ማኅበረ በዓለ ወልድ ሰሜን አሜሪካ

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

አንድ አድርገን

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views

የዋልድባ ገዳም ታሪካዊ፣ ጥንታዊ፣ ቅዱስ የጸሎት እና ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታ ነው። ቅድስናውንም ከሰው የተሰጠው ሳይሆን በመድኅኒታችን በመድኅኒዓለም ክርስቶስ የተሰጠው ስለሆነ ቦታው ቅዱስ ነው፥ ቅድስናውን ጠብቀን ለትውልድ ማውረስ የእኛ ዋነኛ ዓላማችን ነው።

dejeselam

4 out of 5 dentists recommend this WordPress.com site

Follow

Get every new post delivered to your Inbox.

Join 932 other followers

%d bloggers like this: